Asset Publisher

null በሀገራዊ እና ተቋማዊ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

በሀገራዊ እና ተቋማዊ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ  ውይይት ተካሄደ፡፡

 

ህዳር 20/2016 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር )፣ የሰላም ሚኒስቴር አመራርና ሰራተኞች በሀገራዊ እና ተቋማዊ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ  ውይይት አካሂደዋል ፡፡

 

በመድረኩ ሀገራዊና ተቋማዊ የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በሰላም ሚኒስቴር የስትራቴጂክ ጉዳዬች ሥራ አስፈፃሚ አቶ አዱኛ በቀለ አማካኝነት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

 

የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር አቶ ታዬ ደንደአን ጨምሮ የተቋሙ ሰራተኞ በውይይት መድረኩ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡