''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የሰላም ሩጫ በሰላም ተጠናቋል
Nested Applications
Asset Publisher
ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም. መነሻውን በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በማድረግ በባምቢስ ፣ በዑራኤል አደባባይ ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ መጨረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው የሰላም ሩጫ ተጠናቋል።
በሰላም ሩጫው ላይ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ የውጭ ሁገር ዲፕሎማቶችና አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እና የኃይማኖት አባቶች በሰላም ሩጫው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
የሰላም ሩጫው ዓላማ በሀገራችን የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም የበለጠ እንዲያጠናክር ለማድረግ እና መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ሰላም በጋራ እንዲሰሩ መነሳሳትን ለመፍጠር ያለመ ከመሆኑም ባሻገር እኛ ኢትዮጵያውያን ለሰላም የምንሰጠውን ዋጋና ለሰላም ያለንን ፍላጎት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ መሆኑን ተገልጿል። በሩጫው በሴቶች እና በወንዶች ተወዳድረው 1-3 ላሸነፉ አትሌቶች ሽልማት ተበርክቶላቸል።
በመጨረሻ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም እና በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ በኩል ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የሰላም ሩጫው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በተመረጡ ከተሞች ተካሂዷል።
Nested Applications
Asset Publisher
አዳዲስ ዜናዎች
Asset Publisher
ትንታኔ
ባህላዊ ግጭት አፈታት ስርአቶች ለሰላም ያላቸው ፋይዳ
በሀገራችን የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች ያሏቸውን የግጭት አፈታት ስርአቶች ብንመለከት ግጭት ውስጥ በገቡ ወገኖች መካከል እርቅ እንዲወርድ በማድረግ የተወሰነ ሳይሆን፤ ለግጭት ዘላቂ መፍትሄ በመፈለግ በማህበረሰቡ ዘንድ በግጭቶች ምክንያት ደፍርሶ የነበረውን ሰላም መልስ እስኪያገኝ ድረስ የሚዘልቅ ሲሆን በዚህም በግጭት ምክንያት የተቋረጡ ማህበራዊ ግንኙነቶቻቸውን በመጠገን በማህበረሰቡ ዘንድ ዘላቂ የሆነ ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖር ያደርጋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡፌዴራሊዝም እና የፌዴራል ሥርዓት
የፌደራሊዝም እና መንግስታት ግንኙነት መነሻ የፌደራል ስርአቱን አሰመልክቶ ከፌዴራል መንግስት የሚተላለፍ ትዕዛዝና ጥያቄ፣ ከክልሎች የሚቀርብ ጥያቄ እንዲሁም ከተለያዩ የመንግስታት ግንኙነት ፎረሞችና የምርምር ውጤቶች የተገኙ መረጃዎችና የተለዩ ችግሮችና ክፍተቶች ሊሆን ይችላል፡፡ መድረሻውም እነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ አግኝተውና ክፍተቶቹና ችግሮቹም ተቀርፈው የተመሰረተ ጠንካራና ቀጣይነት ያለው የፌደራል ስርአት እና መንግስታት ግንኙነት ተግባራዊ ማድረግ ይሆናል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ