የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ከተባባሩት መንግስታት ልማት ፕርግራም /UNDP/ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

የካቲት 27/2017 ዓ.ም (ሰላም ሚኒስቴር)፣ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ ከተባባሩት መንግስታት ልማት ፕርግራም /UNDP/ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሰላም ግንባታ ሥራዎችን መሠረት አድርገው ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይታቸውም የሰላም ሚኒስቴር እያከናወናቸው ስላሉ ተግባራት በተለይም ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ብሔራዊ መግባባትን ለማጎልበት እና መሰረታዊ የሀገር መንግስት ግንባታ ሥራዎች እንዲጠናከሩ ለማድረግ የሚያስችሉ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡

ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ አክለውም የሰላም ሚኒስቴር የዘላቂ ሰላም ስራዎችን እና የብሔራዊ መግባባት ተግባራትን ለማጎልበት በሰላም ዙሪያ ከሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥት ልማት ድርጅት ከዚህ በፊት የሰላም ግንባታ ሥራዎችን ለመደገፍ ስለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ልማት ድርጅት ተወካይ ሚስተር ሳሙኤል ዱይ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበልና ገለፃ አመስግነው በትብብር ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ቀልጸዋል። ቀጣይም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለመደገፍ የጋራ ቴክኒካል ቡድን አቋቁመው አብሮ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡