በብሔራዊ ጥቅሞችና ቀጣናዊ ትስስር ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የውይይት መድረክ ተካሄደ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር) የሰላም ሚኒስቴር ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር "ብሔራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የህዝቦች ተጠቃሚነት" በሚል ርዕስ ውይይት አካሂዷል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ እንደተናገሩት እሳቸውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ ሰዓት ሰላምን እጅግ እንደሚፈልግ ተናግረዋል :: ሀገር ብዙ ኢንቨስት አድርጋ ያስተማረችው ምሁር ስለ ሃገሩ ዕጣ ፈንታና ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለማስከበር መሄድ ያለብን በምን አቅጣጫ እንደሆነ ወሳኝ ምክረሃሳብ ማቅረብ መብት ሳይሆን ብሔራዊ ግዴታው ነው ብለዋል::

May be an image of 2 people and people studyingበሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ዳኘ ሽብሩ (ዶ/ር )ለውይይት መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሃሳቦችና ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል::

May be an image of 4 people and textየዕለቱ የክብር እንግዳ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የተከበሩ አቶ ጅሀድ ናስር የውይይት መድረኩ ዓላማ የአንድ ቀን ምክክር ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ሰላምን ለመገንባትና የህዝቦችን ሚዛናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የምሁራን ሚና ምን ሊሆን እንደሚችል፣ መንግስትም ሆነ በተቃራኒው ጎራ ያሉ አካላት የሀገርን አንድነት ለማጠናከርና ለቀጣናው ፖለቲካ አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ ብሎም ኢትዮጵያ የራሷን ጥቅሞች የምታስከብርና ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀገር እንድትሆን ለማስቻል ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ምሁራን በእውቀት የተደገፈ ሃሳብና አቅጣጫ እንዲያመላክቱ ይፈለጋል ብለዋል::

May be an image of 1 person and newsroomበሰላም ሚኒስቴር በሀገር ግንባታ ዘርፍ የብሄራዊ መግባባት ከፍተኛ ባለሙያ ወ/ሮ ሲሳይ ብርሌ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሀገር ግንባታ አንፃር ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር የተለያዩ የምክክር መድረኮች በማዘጋጀት በመሥራት ላይ እንደሆነ ጠቁመው የዛሬው መድረክም ጠቃሚ ምክረ ሀሳቦች የተገኙባቸው መሆኑ አንስተዋል::

ምንጭ:- ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ