ዓለም አቀፍ የኃይማኖት ኮንፈረንስ የፎቶ ኤግዚቪሽን
Aplicações Aninhadas
Publicador de Conteúdos e Mídias
የሰላም ሚኒስቴር ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ከሚገኘው ከመሐመድ ቢን ዛይድ ፎር ሁማኒቲ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር እየተካሄደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ኮንፈረንስ ላይ ሀገራችን ያላትን የረጅም ዘመናት የሃይማኖት መከባበርና አብሮነት ለዓለም ለማሣየትና ለማስገንዘብ ያለመ የፎቶ ኢግዚቢሽን ተዘጋጅቷል ።
የፎቶው ኢግዚቢሽኑ በኢፌድሪ ፕሬዚዳንት ክቡር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ፣ በሰላም ሚኒስቴር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም እና በሐይማኖት አባቶች ተመርቆ ተከፍቷል።
የሰላም ሚኒስቴርን ጨምሮ የኢትዮጵያ የሃይማኖቶች አባቶች ፣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ፣የክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊዎች፣በሐይማኖት እና ሰላም ላይ ትኩረት አድርገው ጥናትና ምርምር ያካሄዱ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምስራቅ አፍሪካ፣ የሩሲያ፣ የሞሮኮ እና የደቡብ አፍሪካ የሃይማኖት ተቋማት እና አለም አቀፍ ድርጅቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በኮንፈረንሱ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
Publicador de Conteúdos e Mídias
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪAplicações Aninhadas
Publicador de Conteúdos e Mídias
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ