የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ አሰጠጣ ሥርዓት ለማዘመን የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አምባሳደር ክቡር ሞሐመድ ሳሌም አል-ራሽዲን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ
Aplicaciones anidadas
Publicador de contenidos
Publicador de contenidos
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪAplicaciones anidadas
Publicador de contenidos
መስከረም 8/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ የሰላም ሚኒስቴር የአሠራር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት ለመሥራት በሚቻልበት አቅጣጫ ከአጋር ድርጅቶችና ተቋማት ከተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
የሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ በሰጡት ማብራሪያ፡- ግጭት በሰው ልጅ መካከል በሚኖር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት መሠረት አድርጎ ሊከሰት የሚችል ተፈጥረዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ከመከሰቱ በፊት ቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቅሰው ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የግጭት ቅድመ መከላከል ሥርዓቱን በተደራጀና በዘመነ መንገድ በአጋርነትና በትብብር እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂና ፈጣን ምላሽ አሰጣጡን የዘመነና በጥናት ላይ የተመሠረተ ለማድረግ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሶፍትዌር የማበልፀግ እና በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የመረጃ ቋት (ዳታ ሴት) የመሥራት ፕሮጀክቶች ተጠናቆ ወደ ተግባር እየተገባ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ውጤታማነቱ የላቀ እንዲሆን በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ ለማሳደግ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑ ተገልጿል፡፡
Publicador de contenidos
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡPublicador de contenidos
Publicador de contenidos
መስከረም 20/2017 ዓ.ም (ሰላም ሚኒስቴር)፤ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አምባሳደር ክቡር ሞሐመድ ሳሌም አል-ራሽዲን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቅርብ ግንኙነት በማድነቅ የሰላም ሚኒስቴር በሰላም ግንባታ፣ሰላምን በሚያጠናክሩ እና በሚያጸኑ የተለያዩ ስራዎች ዙሪያ ከሀይማኖት ተቋማት ጋር እንደዚሁም በወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት እያከተከናወኑ ያሉ ተግባራት ዙሪያ ገለጻ ያደረጉላቸው ሲሆን፤ በቀጣይም ሰላምን በሚያጠናክሩ ተግባራት በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ መሰል ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ገልፀዋል።
ክቡር ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) አክለውም ኢምባሲው ወደ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በመምጣት በመጎብኘታቸው አብሮነታቸውን እና ለጋራ ግንኙነቱ የሰጡትን ትኩረት አመስግነዋል።
ክቡር ሞሐመድ ሳሌም አል-ራሽዲን የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አምባሳደር በበኩላቸው ስለተደረገላቸው አቀባበል አመስግነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የልማት ስራ በማድነቅ ሰላምን የማጽናት ስራው አካል በመሆን በወንድማማችነት እና በአብሮነት በመረዳዳት አብረው መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።