የሰላም ሚኒስቴር ከሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ አሰጠጣ ሥርዓት ለማዘመን የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ
内嵌的应用
资产发布器
ሐምሌ 5/2017ዓ.ም (ሰላም ሚኒስቴር) ፤ የሰላም ሚኒስቴር በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡
መድረኩን የከፈቱት የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ እድሪስ የዛሬው መድረክ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማችን ያከናወናቸውን ተግባራት በጥልቀት በመመልከት የተገኙ መልካም ውጤቶችን ለማጠናከር እና ያጋጠሙ ችግሮችን ደግሞ በመፍታት በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ሥራ ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል።
የሰላም ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ያቀረቡት የሰላም ሚኒስትር አማካሪ እና የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ሰውነት ቸኮል የሰላም ሚኒስቴር በ2017 በጀት ዓመት በአወንታዊ ሰላም ግንባታ፣ በሀገር ግንባታ፣ በሰላም የብሔራዊ በጎ ፈቃድ የማህበረሰብ ፕሮግራም፣ በግጭት መከላከልና አስተዳደር፣ በፌዴራሊዝምና የመንግስታት ግንኙነት እንዲሁም በተቋማዊ ሪፎርምና የማስፈፀም አቅምን ለማሳደግ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተገኙ ስኬቶችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

አቶ ሰውንት ቸኮል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን ያቀረቡ ሲሆን የዘንድሮ ዕቅድ በየደረጃው ካሉ አመራሮችና እና ሰራተኛች ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የታቀደ መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ አንኳር ተግባራት ተለይተዋል ብለዋል።
ያሉ ሀገራዊ ዕድሎች እና ስጋቶች በዕቅዱ ውስጥ በጥልቀት ታይተዋል ያሉት አቶ ሰውነት በጀት ዓመት ህዝብን በስፋት የሚያሳትፋ ትልልቅ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ የሰላም የንቅናቄ ሥራዎች ለማከናወን ታቅዷል ብለዋል።
በቀረበው ሪፖርት እና ዕቅድ ከሰራተኞች አስተያየትና ጥያቄ ተነስቶ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
资产发布器
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪ内嵌的应用
资产发布器
መስከረም 8/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ የሰላም ሚኒስቴር የአሠራር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት ለመሥራት በሚቻልበት አቅጣጫ ከአጋር ድርጅቶችና ተቋማት ከተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
የሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ በሰጡት ማብራሪያ፡- ግጭት በሰው ልጅ መካከል በሚኖር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት መሠረት አድርጎ ሊከሰት የሚችል ተፈጥረዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ከመከሰቱ በፊት ቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቅሰው ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የግጭት ቅድመ መከላከል ሥርዓቱን በተደራጀና በዘመነ መንገድ በአጋርነትና በትብብር እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂና ፈጣን ምላሽ አሰጣጡን የዘመነና በጥናት ላይ የተመሠረተ ለማድረግ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሶፍትዌር የማበልፀግ እና በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የመረጃ ቋት (ዳታ ሴት) የመሥራት ፕሮጀክቶች ተጠናቆ ወደ ተግባር እየተገባ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ውጤታማነቱ የላቀ እንዲሆን በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ ለማሳደግ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑ ተገልጿል፡፡
资产发布器
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ