资产发布器

null የሰላም ሚኒስቴር ከሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ

ሐምሌ 5/2017ዓ.ም (ሰላም ሚኒስቴር) ፤ የሰላም ሚኒስቴር በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡

መድረኩን የከፈቱት የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ እድሪስ የዛሬው መድረክ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማችን ያከናወናቸውን ተግባራት በጥልቀት በመመልከት የተገኙ መልካም ውጤቶችን ለማጠናከር እና ያጋጠሙ ችግሮችን ደግሞ በመፍታት በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ሥራ ለመስራት ያለመ ነው ብለዋል።

የሰላም ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ያቀረቡት የሰላም ሚኒስትር አማካሪ እና የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ሰውነት ቸኮል የሰላም ሚኒስቴር በ2017 በጀት ዓመት በአወንታዊ ሰላም ግንባታ፣ በሀገር ግንባታ፣ በሰላም የብሔራዊ በጎ ፈቃድ የማህበረሰብ ፕሮግራም፣ በግጭት መከላከልና አስተዳደር፣ በፌዴራሊዝምና የመንግስታት ግንኙነት እንዲሁም በተቋማዊ ሪፎርምና የማስፈፀም አቅምን ለማሳደግ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተገኙ ስኬቶችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

አቶ ሰውንት ቸኮል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን ያቀረቡ ሲሆን የዘንድሮ ዕቅድ በየደረጃው ካሉ አመራሮችና እና ሰራተኛች ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የታቀደ መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ አንኳር ተግባራት ተለይተዋል ብለዋል።

ያሉ ሀገራዊ ዕድሎች እና ስጋቶች በዕቅዱ ውስጥ በጥልቀት ታይተዋል ያሉት አቶ ሰውነት በጀት ዓመት ህዝብን በስፋት የሚያሳትፋ ትልልቅ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ የሰላም የንቅናቄ ሥራዎች ለማከናወን ታቅዷል ብለዋል።

በቀረበው ሪፖርት እና ዕቅድ ከሰራተኞች አስተያየትና ጥያቄ ተነስቶ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

访问最多的资产

null ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች "ላይ የተካሄደ ጥናት ውጤት ይፋ ተደረገ

ኅዳር 23/2016 . (የሰላም ሚኒስቴር)፣ "ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች "ላይ የተካሄደ ጥናት ውጤት ይፋ የማድረግ መርሃ -ግብር ተካሄዷል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ታዬ ደንደአ በሀገራችን 2010 . እስከ 2015 . ድረስ በተለያዩ ክልሎች በተለያዩ ምክንያቶችና የግጭት መንስኤዎች የሚከሰቱ ግጭቶች ወደ ሁከትን እና ብጥብጥ አድገው ከፍተኛ ጉዳት በሰውና በንብረት ሲያደርሱ ቆይተዋል፤ እያደረሱም ነው ብለዋል፡፡

የሰላም ሚኒስቴር እነዚህ የሚስተዋሉ ግጭቶችንና አለመግባባቶችን ለመፍታት በተናጠል ከመስራት ማህበረሰባዊ ለውጥ ሊያመጣ በሚያስችል መንገድ ሁሉንም ዜጎችና ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ጥናቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል በማለት ክቡር ሚኒስትር ደኤታው ገልፀዋል  ፡፡

አክለውም በዛሬው ዕለት ይፋ የሚደረገው ጥናት ዋና ዓላማ እና አስፈላጊነት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ ግጭቶች መንስዔዎቻቸውን በመለየት፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ስርዓትን በመዘርጋት ግጭቶችን ከመከሰታቸው በፊት መከላከል፣የህብረተሰቡን በሰላም የመኖር ልምድ በመጠቀም እና የሚከሰቱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት የዘላቂ መፍትሄ አማራጮችን መጠቆም ነው ብለዋል ፡፡

''ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች'' በሚል ርዕስ ጥናት ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጰያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተባባሪ ፕሮፌሰር እና የምርምር  ክፍል ኃላፊ የሆኑት / ደሳለኝ አምሳሉ  ናቸው።

/ ደሳለኝ በጥናታቸው በኢትዮጵያ (2018-2022 ..) የተከሰቱ ግጭቶች መንስኤዎችና የመፍትሄ ሃሳቦችን በዝርዝር  አስቀምጠዋል።

ጥናቱ በኢትዮጵያ የተነሱ ግጭቶች በየትኞቹ የሀገራችን ክፍሎች በብዛት ተስተዋል የሚለውን የሚያሳይ የግጭት ፍኖተ ካርታ/conflict mapping/ የያዘ ሲሆን የተከሰቱ ግጭቶች መሰረታዊ እና አባባሽ ምክንያቶችን እና ምን ቢደረግ ግጭቶች ሊቀንሱ ይችላሉ ሚለውን ሃሳብ አስቀምጧል።

በሰላም ሚኒስቴር የፌዴራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር / ስዩም መስፍን የሰላም ሚኒስቴር በተሰጠው ስልጣን መሰረት ግጭቶች መንስኤዎችን አጥንቶ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በጥናት ለይቶ የማቅረብ ስራ እንደሚሰራ ገልፀው ዛሬ ይፋ የተደረገው ጥናት ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት በጋር በመሆን የተካሄደ እንደሆነ እና ከትግራይ ክልል በስተቀር ጥናቱ ሁሉንም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ያካተተ መሆንንአስገንዝበዋል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የሰላምና የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አመራሮችና የኮሚቴ አባላት ፣የሰላም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ፣የፌዴራልና የክልል የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እና የባለድርሻ አካላት አመራሮች በፕሮግራሙ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡