የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ አሰጠጣ ሥርዓት ለማዘመን የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ
Beágyazott alkalmazások
Tartalom megjelenítő
Tartalom megjelenítő
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪBeágyazott alkalmazások
Tartalom megjelenítő
መስከረም 8/2018 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ የሰላም ሚኒስቴር የአሠራር ሥርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት ለመሥራት በሚቻልበት አቅጣጫ ከአጋር ድርጅቶችና ተቋማት ከተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
የሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ በሰጡት ማብራሪያ፡- ግጭት በሰው ልጅ መካከል በሚኖር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት መሠረት አድርጎ ሊከሰት የሚችል ተፈጥረዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ከመከሰቱ በፊት ቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቅሰው ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የግጭት ቅድመ መከላከል ሥርዓቱን በተደራጀና በዘመነ መንገድ በአጋርነትና በትብብር እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂና ፈጣን ምላሽ አሰጣጡን የዘመነና በጥናት ላይ የተመሠረተ ለማድረግ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሶፍትዌር የማበልፀግ እና በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የመረጃ ቋት (ዳታ ሴት) የመሥራት ፕሮጀክቶች ተጠናቆ ወደ ተግባር እየተገባ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ውጤታማነቱ የላቀ እንዲሆን በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ ለማሳደግ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑ ተገልጿል፡፡
Tartalom megjelenítő
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ