''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የሰላም ሩጫ በሰላም ተጠናቋል
Nested Applications
Asset Publisher
ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም. መነሻውን በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በማድረግ በባምቢስ ፣ በዑራኤል አደባባይ ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ መጨረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው የሰላም ሩጫ ተጠናቋል።

በሰላም ሩጫው ላይ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ የውጭ ሁገር ዲፕሎማቶችና አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እና የኃይማኖት አባቶች በሰላም ሩጫው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
የሰላም ሩጫው ዓላማ በሀገራችን የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም የበለጠ እንዲያጠናክር ለማድረግ እና መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ሰላም በጋራ እንዲሰሩ መነሳሳትን ለመፍጠር ያለመ ከመሆኑም ባሻገር እኛ ኢትዮጵያውያን ለሰላም የምንሰጠውን ዋጋና ለሰላም ያለንን ፍላጎት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ መሆኑን ተገልጿል። በሩጫው በሴቶች እና በወንዶች ተወዳድረው 1-3 ላሸነፉ አትሌቶች ሽልማት ተበርክቶላቸል።
በመጨረሻ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም እና በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ በኩል ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የሰላም ሩጫው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በተመረጡ ከተሞች ተካሂዷል።
Asset Publisher
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪNested Applications
Asset Publisher
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ