''ሰላም  ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የሰላም ሩጫ በሰላም ተጠናቋል

Nested Applications

Asset Publisher

null ''ሰላም  ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የሰላም ሩጫ በሰላም ተጠናቋል

ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም. መነሻውን በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በማድረግ በባምቢስ ፣ በዑራኤል አደባባይ ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ  መጨረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው የሰላም ሩጫ ተጠናቋል።

በሰላም ሩጫው ላይ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ የውጭ ሁገር ዲፕሎማቶችና አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እና የኃይማኖት አባቶች በሰላም ሩጫው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የሰላም ሩጫው ዓላማ በሀገራችን የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም የበለጠ እንዲያጠናክር  ለማድረግ እና መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ሰላም በጋራ እንዲሰሩ መነሳሳትን ለመፍጠር  ያለመ  ከመሆኑም ባሻገር እኛ ኢትዮጵያውያን ለሰላም  የምንሰጠውን ዋጋና ለሰላም ያለንን ፍላጎት  ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ መሆኑን ተገልጿል። በሩጫው በሴቶች እና በወንዶች ተወዳድረው 1-3 ላሸነፉ አትሌቶች ሽልማት ተበርክቶላቸል።

በመጨረሻ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም እና በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ በኩል ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

የሰላም ሩጫው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በተመረጡ ከተሞች ተካሂዷል።

Asset Publisher

የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት

አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር

የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።

ተጨማሪ

Nested Applications

Asset Publisher

ትንታኔ

ማህበራዊ ሀብቶቻችን ለሀገራዊ ሰላም

ማህበራዊ ሀብቶቻችን የአብሮነት፣ የሰላምና መቻቻል የትስስር ሰንሰለት ተምሳሌት ከመሆናቸው ባለፈ ለህዝቦች አብሮ መኖርና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም ግንባታ ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

የሀገረ ብሔር ግንባታ/ Nation Building ምንነት

ሀገረ ብሔር ግንባታ/Nation Building/ ስንል በአንድ ሀገር የሚኖሩ ህዝቦች የጋራ ማንነታቸውን፣ የጋራ አመለካከታቸውን ፣ እምነታቸውንና የጋራ እሴታቸውን የሚገነቡበትና የሚያዳብሩበት ሂደት ነው፡፡ ይህም በአንድ ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ካለፈው ታሪካቸው እና ከአሁኑ የጋራ አኗኗራቸው የመነጨ የጋራ አመለካከት እሴቶችና እምነቶች የሚገነቡበት እና ከሌሎች ጎረቤት ሀገራትና ህዝቦች የሚለያቸው የጋራ መለያ ባለቤት የሚሆኑበት ሂደት ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

Asset Publisher

ቪዲዮ ዜና

በጎነት ለአብሮነት
በጎነት ለአብሮነት
final The Vanguard of Peace
ባህላዊ የግጭት አፈታት