''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም'' በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው የሰላም ሩጫ በሰላም ተጠናቋል
Nested Applications
Asset Publisher
ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም. መነሻውን በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በማድረግ በባምቢስ ፣ በዑራኤል አደባባይ ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ መጨረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው የሰላም ሩጫ ተጠናቋል።
በሰላም ሩጫው ላይ ክቡራን ሚኒስትሮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ የውጭ ሁገር ዲፕሎማቶችና አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ እና የኃይማኖት አባቶች በሰላም ሩጫው ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
የሰላም ሩጫው ዓላማ በሀገራችን የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም የበለጠ እንዲያጠናክር ለማድረግ እና መላው ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ሰላም በጋራ እንዲሰሩ መነሳሳትን ለመፍጠር ያለመ ከመሆኑም ባሻገር እኛ ኢትዮጵያውያን ለሰላም የምንሰጠውን ዋጋና ለሰላም ያለንን ፍላጎት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ መሆኑን ተገልጿል። በሩጫው በሴቶች እና በወንዶች ተወዳድረው 1-3 ላሸነፉ አትሌቶች ሽልማት ተበርክቶላቸል።
በመጨረሻ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱአለም እና በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ በኩል ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የሰላም ሩጫው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በተመረጡ ከተሞች ተካሂዷል።
Asset Publisher
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪNested Applications
Asset Publisher
ትንታኔ
ማህበራዊ ሀብቶቻችን ለሀገራዊ ሰላም
ማህበራዊ ሀብቶቻችን የአብሮነት፣ የሰላምና መቻቻል የትስስር ሰንሰለት ተምሳሌት ከመሆናቸው ባለፈ ለህዝቦች አብሮ መኖርና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም ግንባታ ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡየሀገረ ብሔር ግንባታ/ Nation Building ምንነት
ሀገረ ብሔር ግንባታ/Nation Building/ ስንል በአንድ ሀገር የሚኖሩ ህዝቦች የጋራ ማንነታቸውን፣ የጋራ አመለካከታቸውን ፣ እምነታቸውንና የጋራ እሴታቸውን የሚገነቡበትና የሚያዳብሩበት ሂደት ነው፡፡ ይህም በአንድ ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ካለፈው ታሪካቸው እና ከአሁኑ የጋራ አኗኗራቸው የመነጨ የጋራ አመለካከት እሴቶችና እምነቶች የሚገነቡበት እና ከሌሎች ጎረቤት ሀገራትና ህዝቦች የሚለያቸው የጋራ መለያ ባለቤት የሚሆኑበት ሂደት ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ